tg-me.com/ethio27/87
Last Update:
"Less less politics more more economics "
~~~
የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ውስጥ ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ ከተደረጉት 3 የብሔረሰብ ዞኖች አንዱ ነው። ዞኑ ከክልሉ ዋና ከተማ ባህርዳር በደቡባዊ ምዕራብ አቅጣጫ በ122 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። የብሔረሰብ አስተዳደሩ መቀመጫ የሆነችው እንጅባራ ከተማ ደግሞ ከአዲስ አበባ ባህርዳር መንገድ በ435 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ መገኛዋ ነው።
የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር
#በምስራቅ- የምዕራብ ጐጃም ዞን፣
#በምዕራብ- የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣
#በሰሜን- የሰሜን ጎንደርና ምዕራብ ጐጃም ዞኖች፣
#በደቡብ- ምዕራብ ጐጃምና የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልል ያዋስኑታል።
የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር የበርካታ ታሪካዊና ተፈጥሮአዊ መስህብ ሀብቶች፣ የባህል እሴቶችና ማህበራዊ ኩነቶች ባለቤት ነው። የተለያዩ ውሃማ አካሎች በጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ ትልልቅና መለስተኛ ወንዞች፣ ምንጮች፣ እርጥበት አዘል ባህር ሸሸ መሬቶች፣ ፏፏቴዎችና ሐይቆች የተመልካችን ቀልብ ሊስቡ የሚችሉ ውብና ማራኪ የቱሪስት መስህብ ሀብቶች መገኛ ነው። ማን ለሕዝቡ ጥቅም የውል? (የአዊ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ግን በሕይወት አለ? ከናይጄሪያ ነው ከቡልጋሪያ መጥተው እስኪያለሙልህ ነው የምትጠብቀው?) ዋታ ኩ ዲቪ?
ረጅም ዕድሜ ያስቆጠሩ በርካታ ገዳማት፣ አድባራትና አብያተ ክርስቲያናት፣ መካነ-መቃብሮችና ዋሻዎች፣ የብራና መጽሐፍት እንዲሁም ጥቅጥቅ የተፈጥሮ ደኖች፣ በርካታ የዱር እንስሳትና አዕዋፍ ዝርያዎች መገኛ ነው። ለአብነት የዘንገናና የጥርባ ሃይቅ፣ የትስኪ፣ የዶንደር፣ የፋንግና የጋርቾ ፏፏቴ፣ የዳንጉላ ዋሻና የወለተ ጴጥሮስ ገዳምን በጥቂቱ መጥቀስ ይቻላል። ይህ ሀብት ታዲያ የትኛው ስትራቴጅክ አመራር ወደ ገቢ ምንጭነት የቀረው?
ብሔረሰቡ ተቀድቶ የማያልቅ ባህል፤ የራሱ ቋንቋና በኢትዮጵያ ታሪክ አስተዳደራዊ ድርሻ የነበረው ቀደምት ህዝብ ነው አገው፡፡
አዊ ዞን እንፊዲ፣አሰም፣ዚሪኺ፣ገምበሃ እና ቓዣ ከሚባሉ ተራሮችና ሰንሰለታማ ጋራዎች በስተቀር ሜዳማና ለም ነው።የአዊ-አገው ሕዝብ በሰሌን ጥላ፣ በፈረስ እርሻ፣ በአካባቢ ጥበቃና ልማት ይታወቃል። በአዊ አካባቢ በውሀ ሀብት በኩል ጥቅም ሊውሉ የሚችሉ በርካታ ወንዞችና ሀይቆችም ይገኛሉ።ለምሳሌ ፣አዩ፣ዱራ፣አጣም፣ዲም፣ግዛኒ፣አርዲ የተባሉና ሌሎች ወንዞች ትስኪ፣ፋንግ፣ጋርቾ የተሰኙ ፏፏቴዎች ዚምቢሪ፣ዘንገና እና ጥርባ የመሳሰሉ ሃይቆች ይገኙበታል።ማልማት ለሚችል ባለሀብት ምቹ አጋጣሚ አለ።
ሌላው በአዊ ዘንድ የሚታወቀው የ‹‹አዊት ድጋግ›› ወይም "የአገው ዣን ጥላ" ነው።አዊት ድጋግ የአገው መገለጫ ልዩ ማህተም ነው። ዘንገና እንደምታዩት በከፍታ የመልክአ-ምድር ወለል ላይ የሚገኝ አስደማሚ የተፈጥሮ ውበት ነው።ዘንገና ሐይቅ 16ዐ ሜትር ጥልቀት አለው።በሀይቁ አቅራቢያ በደን የተሸፈኑ ተራሮችና በርካታ ዋሻዎች ይገኛሉ፡፡ከፍተኛ የቱሪዝም ምንጭ የሚሆኑ የተፈጥሮ ሀብቶች መገኛ ነው አገው ምድር! ነገር ግን ይህን በተፈጥሮ ፀጋ የታደለ ምድር በማንና እንዴት ይልማ? ይህ ሊያሳሰበን ይገባል! ኖጂ እንፃኽስትናውላስ አይ ይንታምባይ?
እርግጥ እየተሰራ ያሉ ጥቂት ስራዎችን እውቅና ሳንነፍግ ማለት ነው! የብሔሰቡ አስተዳደር ከእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ መቋቋምና በተፋጠነ ሁኔታ ወደ ስራ መግባት ጋር ተያይዞ ተጨማሪ የመልማት ዕድልን ከመጎናፀፉ ባሻገር በተለይ የእንጅባራ ከተማ እድገት ላይ በጎ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል። በስራ ዕድል ፈጠራንም እያገዘ ይገኛል። ይሁን እንጂ አዊ አሁንም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የተማረ ስራ-ዓጥ የያዘ፣በቂ መሰረተ ልማት ያልተዘረጋለት አካባቢ ነው። በተፈጥሮና ከተቸረው ፀጋ አኳያ ግን አሁን ትልቅ የመልማት አቅም ያለው ነገር ግን በአግባቡ ያልለማ አካባቢም ነው። ይህ ቁጭትን ሊጭር ይገባል። ብዙ ግዜ በክልሉ ከሚመደበው በጀት ጋር ተያይዞ የሚነሳ ቅሬታ መኖሩን ባውቅም የብሔረሰብ አስተዳደሩ በተሰጠው ስልጣን በራሱ መስራት የሚችላቸውን በርካታ ተግባራት እንኳ በቸልተኝነት የሚመለከት ነው። በነገራችን ላይ በአማራ ክልል ሕገ-መንግስት መሠረት ለብሔሰብ ምክር ቤቱ የተሰጡ ስልጠንና ተግባራትን ብትመለከቱ ከክልሉ ምክርቤት ያልተናነሰ ሰፊ ስልጣን ያለው ነው።
ለምሳል ብሔረሰብ አስተዳደሩ በሚከተሉት ጉዳዮች የክልሉን መንግስት መውቀስ አይችልም!
፤
ሀ) በብሔረሰብ አሰተዳደሩ ስር የሚገኙ የዞኑ፣የወረዳ፣የከተማ አስተዳደር የመንግስት የስራ አስፈፃሚዎችን ሹመት፣(ማን መክሮ ዘክሮ አፅድቆ እንደሚልክ የሚታወቅ ስለሆነ) የመሰለውን መርጦ መላክ ስልጣን ተሰጦታልና!
ለ)የብሔረሰብ ምክር ቤት አባላት ምርጫ፣ (በሕዝብ የተመረጡ ስለሆኑ) የሚጠቅምህን መምረጥ መብትህ ነውና!
ሐ) በብሔረሰብ አስተዳደሩ አቅም በሚሰሩ ጉዳዮች( በተሰጠው ውስን በጀትም ቢሆን መለስተኛ ልማቶች ማከናወን፣የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት፣ አገውኛ ቋንቋን ማሳደግ፣ ማበልፀግ ፣ባህሉን፣ታሪኩን ማስተዋወቅ ማሳደግ ወዘተ) እና ሌሎች መሰልጉዳዮችን በተመለከተ ለምን የክልሉን መንግስት ትወቅሳለህ? ኢክስተርናላይዝ ሳናደርግ ወደ ውስጥ እንመልከት! አካባቢውን እናልማ! ድህነትን የሚጠላ ማህበረሰብ እየበዛ፣ ፖለቲከኛ ብቻ ሳይሆን አልሚ አዕምሮዎች መበራከት አለባቸው! ለአዊ ውድቀትም ስኬትም ከታች እስከ ላይ ከሚገኙ የአዊ አመራሮች የተሻለ ሀላፊነት የሚወስድ ማነው? ማንም! ዘመኑን የዋጀ ጠንካራና ስትራቴጅክ አመራሮች እንደ ክልልም እንደዞንም ያስፈልጉናል!ትልቅ አቅም ያላቸው ምሁራን ወጣቶች አሉን እነሱ ወደ ፊት ይምጡ፣ ከምንም በላይ ግን ልማት የሕልውና ጉዳያችን ነው፤ ኢኮኖሚህን በአስተማማኝ መሠረት ላይ ከገነባህ የትኛውም ማዕበል አያናውጥህም! ከፖለቲካው ይልቅ ኢኮኖሚያዊ መበልፀጉ ላይ የሞት ሽረት ትግል ያስፈልጋል! ሁላችንም የራሳች በጎ አሻራ እናሳርፍ! ኬሻቲውማ ይዛኺ? "
ጜዋና ሳሳርስኹሳ ዳንዴ እድ ዋና ቼቫላላ"ናኑ ሴን ዝኮ!
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1158866740982672&id=999060470296634
BY ስለአገው ህዝብ ይመለከተኛል
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280
Share with your friend now:
tg-me.com/ethio27/87